Skip to content
የላ/ጋ/ወ/አስ/ጽ/ቤት የሚያቅዳቸውን እቅዶች በተሟላ መልኩ ለመፈጸምና በስራ ላይ ለማዋል የሚከተለውን በስራ መርሆዎችና እሴቶች ይከተላል
- በወረዳችን በየደረጃው እና በሁሉም ሴክተሮችና የስራ መስኮች ብቃት ያለው አመራር ለመፍጠር ጠንክረን እንሰራለን
- ህዝባዊ ወገንተኝነታችንን በስራ እናረጋግጣለን፣
- የወጡ የመንግስት ደንቦች ፣ ህጎች ፣ መመሪያዎች በፍትኃዊነት በአግባቡ በሁሉም መስክ እንዲተገበሩ እንሰራለን፣
- የህገ የበላይነትን እናከብራለን፣
- የባለጉዳዮችን ጥያቄ በህጋዊ መንገድ በጥሞናና በትህትና አዳምጠን ፣ ወቅታዊና ተገቢ ምላሽ እንሰጣለን
- በእኩልነት ላይ የተመሰረተ የስርአተ ፆታ መርህን እንከተላለን
- የህብረተሰቡንና የመ/ቤቱን ሰራተኞች ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ ያረጋገጠ አስራር እንከተላለን፣
- የግለሰቦችን ጥረትና ተነሳሽነት እንዲጎለብት ጠክረን እንሰራለን፣
- ተደጋግፎ የመስራት ባህልና መተማመን በመ/ቤቱ ውስጥ እንዲሰፍን እናደርጋለን፣
- የግለሰብና የቡድን መብትን እናከብራለን
- የሴቶችን ፍትሀዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን ፣
- ስርዓተ-ጾታን ማዕከል ያደረገ ግንዛቤ እንፈጥራለን